ዓላማ
የዚህ የግል እና የቡድን ማጥኛ እና መወያያ መልዕክት ዓላማ አለው፡፡ ዓላማውም ወጣቶች በግላቸው በማጥናት የህይወት መንገዳቸውን ቀና እና የሰመረ እንዲያደርጉና በተጨማሪም በግሩፕ በመወያየት የተለያዩ እይታዎችን በማስተናገድ መረዳታቸውን እንዲለጥጡ አስተሳሰባቸውንም በብዙ ምክሮች እንዲገነቡ ለማድረግ ነው፡፡
በመቀጠልም ሰዎች ያስተማሯቸውን እና ያሏቸውን ብቻ በመቀበል መረዳታቸውን በዚያው ወስነው እንዳይቀሩ ራሳቸውም አዕምሮአቸውን ከፍተው በማሰብ፤ ዓይናቸውንም ከፍተው በመመልከት ገና ብዙ ያልተገለጡ እውነቶችን እና መገለጦችን ከእግዚአብሔር ቃል በማግኘት ተባርከው ለብዙዎችም በረከት እንዲሆኑ ለማበረታታት ነው፡፡
በሦስተኛ ደረጃም በጋራ የመማማር፣ ሃሳብን በጋራ የማፍለቅ፣ የመደማመጥ፣ የመቀባበል፣ አንዱ ከአንዱ በሚወጣው እይታ እንዲተናነጹና በእውነተኛ ህብረት ውስጥ ያለውን በረከት ለመካፈል፣ ዕውቀት እና መረዳትን ማሳደግ ባህል እንዲያደርጉ፡ አልፎም ያገኙትን መልካም መረዳት ለሰዎች የማካፈል እና ከሌሎችም የመቅሰም ልምድ እና ድፍረትን እንዲያካብቱ ማበረታታት ነው፡፡